pacman, rainbows, and roller s
free book gift

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።


Iqra

=<({አል-ኢኽላስ 112:1-4})>=

ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ


1. በል! እርሱ አላህ አንድ ነው።

2. አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው።

3. አልወለደም፤ አልተወለደምም።

4. ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።
Iqra
Iqra

Homeየወጣቱ ተልዕኮ ምንነትየአቂዳ ትምህርቶችየሶላት መመሪያረመዷንሙስሊም ሴቶችኢስላማዊ ቤተሰብከታሪክ ማህደርሐዲስለወጣቶችትምህርትና መሰረታዊ ክህሎታችጤናችንግጥምጥያቄና መልስኢስላማዊ መዝገበ ቃላት
free book gift

=<({አል-ቁርአን 96:1-5})>=

ያ ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም አንብብ!

free book gift

በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ መሰረት እውቀትን መሻት በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው።

free book gift

ቀዳእ እና ቀድር


በምድርም ሆነ በነፍሶቻችሁ ላይ ምንም መከራ አይገጥማችሁም። ከመከሰቱ በፊት በመፅሐፍ ውስጥ የተፃፈ ቢሆን እንጂ። ብዕሩ ደርቇል ፣ መዝገቡም ተነስቷል ፣ ጉዳዩም ተፈፀመ ፤ ውሳኔዎችም ሁሉ ተፅፈዋል ፤ አሏህ የፃፈልን እንጂ አይነካንም። የሳተህ ነገር አያገኝህም ነበር ያገኘህም አይስትህም ነበር።

ይህ እምነት በነፍስህ ውስጥ ከፀና እና በህሊናህ ውስጥ ከተደላደለ መከራዎች ሁሉ ስጦታ ፣ ፈተናዎች ሁሉ ሽልማቶችና ኒሻኖች ይሆኑልሃል። አሏህ ኸይር ያሻለትን ሰው ይፈትነዋል። ታመምኩ ፣ ልጄ ሞተ ብለህ አትጨነቅ። ከሰርኩ ፣ ቤቴ ተቃጠለ ብለህም አትረበሽ። ፈጣሪህ ወስኗል ፤ ውሳኔውም ተፈፀመ። ምርጫውም እንዲህ ነው። የሚሻለውም አሏህ የመረጠው ነው። ምንዳውም ተገኘ ፤ ወንጀሉም ተማረ። የምስራች መከራ ለደረሰባቸው ሰዎች....... መታገሳቸው እና ሰጭና ተቀባይ ፣ ሰብሳቢ ፣ የሚዘረጋና ስለሚሰራው የማይጠይቅ ፍጡሮቹ ግን የሚጠይቁ የሆነው ጌታቸው የመረጠላቸውን በደስታ በመቀበላቸው ደስ ይበላቸው።

ህሊናህ አያርፍም ፤ ነፍስህም አትረጋም ፤ የልብህ ጉትጎታም አይሰክንም በቀዷና በቀድር እስካላመንክ ድረስ። የምታገኘውንና የሚያጋጥምህን ሁሉ የተፃፈበት የቀድር ብዕር ደረቀ ፤ ስለዚህ በቁጭት ራስህን አትጉዳ። ግድግዳው እንዳይፈርስ መከላከል እችል ነበር ብለህ አታስብ። ውሃው እንዳይፈስ ፣ ነፋስም እንዳይነፍስ ፣ ብርጭቆውም እንዳይሰበር መከላከል ትችል እንደነበር እራስህን አትሸንግል። ይሄ ብፈልግም ብትፈልግም ፣ ባልፈልግም ባትፈልግም ከቁጥጥራችን ውጭ ነው። የተወሰነው ነገር ይከሰታል ፤ የተፃፈውም ተግባራዊ ይሆናል።

አል-ቁርአን 18:29

«የሻም ሰው ይመን የሻም ይካድ»

የቁጣ ፣ የዋይታና ራስን የመውቀስ ወታደሮች ሳይከቡህ በፊት ለቀድር እጅህን ስጥ። የቁጭት ጎርፍ ሳያጥለቀልቅህ በፊት ለቀድር እውቅና ስጥ። ስለዚህ ነገሮች እንዲሳኩልህ ምክኒያቶቹን ከፈፀምክና ዘዴዎችን ከተጠቀምክ በኋላ ግን ደግም ትጠነቀቀው የነበረውን ነገር ቢመጣብህ መሆን የነበረበትና መከሰት የነበረበት እሱ ነውና ራስህን አረጋጋ። «እኔኮ እንዲህና እንዲህ ባደርግ እንዲህና እንዲህ ይሆን ነበር» አትበል ፤ ባይሆን «አሏህ ወሰነ ያሻውንም ፈፀመ» በል።


457

የወጣቱ ተልዕኮ አድራሻ
free book gift

Download Islamic Books
ኢስላማዊ መጽሐፎችን ያውርዱ

Important Web Links


free book gift

free book gift

free book gift

ስለወጣቱ ተልዕኮ ምንነት ለማወቅ እዚህ ላይ ክሊክ ያድርጉ

Copyright©Youth-Mission የወጣቱ ተልዕኮ